ኬ ኬ ኤል-ጄ ኤን ኤፍ ዘላቂነት ፖሊሲ

ኬ ኬ ኤል-ጄ ኤን ኤፍ የዘላቂ ልማት መርህን በመተግበር ቀዳሚ ድርጅት ሲሆን፣ ትርጉሙ በድርጅቱ ስያሜ ውስጥ የሚገኝ ሲሆን "ከረን ካያሜት" ("ካያሙት"ዕብራይስጥኛ ዘላቂነት ማለት ነው) - ይህም ድርጅቱ ያለውን የዓለም ዓቀፍ አካል ያደርገዋል።
በእስራኤል ውስጥ በኬ ኬ ኤል-ጄ ኤን ኤፍ የሚሰጠው የመሬት እና የተፈጥሮ ሀብቶች ምደባ ተፈጥሮ በሚሰጠው “መርህ” ላይ “ፍላጎት” ላይ መሰረት በማድረግ ለወደፊቱ ደግሞ በጥንቃቄ ጥበቃ “መርህ” ላይ የተመሠረተ ነው።

በኬ ኬ ኤል-ጄ ኤን ኤፍ ድርጅት ቅድሚያ ከሚሰጣቸው አካባቢያዊ ጉዳዮች መካከል ዋነኛው የተፈጥሮ ሀብቶችን መጠበቅ እና ለሁሉም የእስራኤል ነዋሪዎች እና ለቀጣይ ትቅልዳቸው የህይወት ጥራትን ማረጋገጥ ነው።

ቀጣይነት ያለው ልማት ከኬ ኬ ኤል-ጄ ኤን ኤፍ ታሪካዊ ሚና የሆነውን የመሬት ጥበቃ እና የመሬት ልማት ለመላው ህዝብ ጥቅም ለዛሬ እና ለነገ ማረጋገጥ ጋር ተስማሜ ነው።

የደን ልማት ዓላማዎች

ኬ ኬ ኤል-ጄ ኤን ኤፍ ፣ በመሬት ልማት ባለስልጣኑ በኩል፣ በ1961 ከመንግስት ጋር በገባው ቃል ኪዳን መሰረት የእስራኤል ህጋዊ የሆነ የደን አስተዳደር ነው። የኬ ኬ ኤል-ጄ ኤን ኤፍ የደን ልማት ፖሊሲ ዛሬ እና ወደፊት ሁሉንም የእስራኤል ዜጎች ለማገልገል የተነደፈ እና በዘላቂ ልማት መርሆዎች ላይ የተመሠረተ ነው።

ከነዚህ መርሆዎች ጋር በሚስማማ መልኩ የኬ ኬ ኤል-ጄ ኤን ኤፍ የደን አስተዳደር የሚከተሉትን ያጠቃልላል

  • ከተፈጥሮ ስነ-ምህዳር ጋር የሚጣጣም እና ስነ-ምህዳራዊ የማይጻረር አካሄድ።
  • ደን ህዝብን እና ማህበረሰቡን የሚያገለግልበት ማህበረሰባዊ አስተሳሰብ።
  • የቱሪዝም ልማትን፣ የግጦሽ እርባታን፣ የእንጨት ኢንዱስትሪዎችን ወዘተ የሚያካትቱ ኢኮኖሚያዊ አጠቃቀሞችን እና ውጥኖችን ማስተዋወቅ።
  • ከትውልድ-ትውልድ እኩልነት መርህ ጋር በጠበቀ መልኩ ደኖችን በነጻ ለህዝብ ክፍት ማድረግ።
  • የእስራኤላውያን ጫካዎች ስፋት እና ጥራታቸው ለወደፊት ትውልዶች ከመጨነቅ አንጻር መጠበቅ።


ኬ ኬ ኤል-ጄ ኤን ኤፍ እስራኤል በደን ልማት እና በአካባቢ ጥበቃ ዘርፍ የፈራረመችባቸውን ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን ለምሳሌ እንደ አጀንዳ 21 እንዲሁም ፀረ-በረሃማነትን፣ ብዝሃ ህይወት ጥበቃ እና ሌሎችም ላይ በጆሃንስበርግ ኮንቬንሽን በተደነገገው እና የተፈረመውን የትግበራ ዕቅድ መሠረት ለመፈፀም ቁርጠኛ ነው።

ኦፍኪም ፓርክ። ፎቶ፡ ታኒያ ሱስስኪንድ፣ ኬኬኤል-ጄኤንኤፍ የፎቶ ማህደር

የደን ልማት ዓላማዎች-

  • የመሬት ገጽታን ማሻሻል እና ብዝሃነቱን ማረጋገጥ።
  • ለህብረተሰቡ የእረፍት፣ የመዝናኛ እና የእግር ጉዞ ቦታዎችን መስጠት።
  • ደኖች የስነ-ምህዳር አገልግሎቶችን እንዲቀጥሉ በማድረግ የእስራኤልን ስነ-ምህዳር እና የተፈጥሮ ሂደቶችን መጠበቅ እና ማጠናከር።
  • በማሕበረሰቡ የሚተከሉ ዛፎችን እንዲጨምር በማድረግ የእስራኤልን ደኖች ጋር ያለውን ግንኙነት ማጠናከር።
  • የደን እና ሌሎች በዛፎች የተተከሉ አካባቢዎችን ኢኮኖሚያዊ አጠቃቀምን ማሳደግ።
  • በኢኮኖሚ ቀውስ ጊዜ ሥራ መፍጠር።
  • የዛፍ እና የዛፍ አካባቢ ጥበቃ.
  • የእስራኤል ክፍት ቦታዎችን በመጠበቅ ላይ ተሳትፎ ማድረግ።


ከእንጨት ምርትም ሆነ ከሌላ ከደን የሚገኘው የገንዘብ ገቢ እንደ ሁለተኛ ደረጃ የደን ጥበቃ ውጤት ይቆጠራል፣ ስለሆነም በእስራኤል ውስጥ የደን ልማት ዋና ዓላማ የገንዘብ ገቢ መሆን የለበትም።

ደኖችን መትከል እና / ወይም ማደኖችን መንከባከብ እንዲሁም የነባር እንጨቶች እንክብካቤ በከፍተኛው ቅልጥፍና እና በተቻለ መጠን ተፈጥሯዊ ሂደቶችን በመጠቀም መተግበር አለበት።

የተተገበሩ የደን ልማት ፖሊሲዎች በደን ልማት እና በስነ-ምህዳር ንድፈ ሃሳቦች በተጨማሪ በእስራኤል ክፍት ቦታዎች አስተዳደር ውስጥ በተከማቹ ሰፊ ተግባራዊ ተሞክሮዎች ላይ የተመሰረቱ መሆን አለባቸው።

ሁሉም የሚጀምረው ከዚህ ነው፡- ኬኬኤል-ጄኤንኤፍ የዛፍ ማቆያ። ፎቶ፡ ታኒያ ሱስስኪንድ፣ ኬኬኤል-ጄኤንኤፍ የፎቶ ማህደር

የዘላቂነት ጽንሰ-ሀሳብ የሚገለጠው ዘላቂ ደኖች ከፕሮፌሽናል የአስተዳደር መርሆች መመስረት ጋር ተያይዞ ነው። በዚህም መሰረት፡-

  • የደን ስብጥርን ለመወሰን በደን በተሸፈነው የደን አከባቢዎች ውስጥ ባሉ የስርዓተ-ምህዳሮች ልዩነት ላይ በመመርኮዝ፥ የዛፎችን ተፈጥሯዊ እድሳት ከፍ ማድረግ ላይ የተመሰረተ ነው።።
  • የደን ተጠቃሚዎቻቸውን እና ሌሎች በደን የሚጠቀሙትን ፍላጎት ለሟሟላት የደን ዓላማዎችን በማካተት እና አካላዊ አቀማመጦችን ከደን ጥበቃ ባለሙያዎች እና ባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር ይደረጋል።
  • በድን ውስጥ የሚደረግው የዛፍ ተከላ እና ጥገና የሚከናወነው ለወደፊቱ አካባቢን በማይጎዳ መልኩ ነው።
  • ተፈጥሮ ስርዓቶች ላይ ጉዳት ሳያስከትል ደኖችን ለመዝናኛ እና ለግጦሽ ይከናወናል።
  • የደን ድብልቅን ሲታቀድ በተቻለ መጠን ቀጣይነት ያለው የአስተዳደር እንቅስቃሴን በመቀነስ በተቻለ መጠን የስነ-ምህዳር ዘላቂነት እና የተፈጥሮ እድሳትን ለመጨመር ዓላማ ያደርጋል።
  • ለወደፊት ትውልዶች ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የእንጨት እና ክፍት ቦታዎች በልማት እንዳይጎዱ አካላዊ, ህጋዊ እና አስተዳደራዊ ጥበቃ ላይ ይደረጋል።
  • የዛፎች ጥበቃ የሚከናወነው የተፈጥሮ ገጽታዎችን እና ቅርሶችን ለመጠበቅ ነው።
  • ቀጣይነት ያለው የአስተዳደር አሠራር መሻሻል በምርምር እና በደን ቁጥጥር ላይ የተመሰረተ ወቅታዊ እውቀት፣ መረጃ እና ልምድ ላይ የተመሰረተ ነው።
ኢላኖት ደን። ፎቶ፡ ታኒያ ሱስስኪንድ፣ ኬኬኤል-ጄኤንኤፍ የፎቶ ማህደር

የእስራኤልን ንጹህ ውሃ ጅረቶችን መመለስ

ኬ ኬ ኤል-ጄ ኤን ኤፍ የእስራኤልን የንፁህ ውሃ ጅረቶች እንደ ተፈጥሯዊ እና ትዕይንት ሀብት እንዲሁም እንደ ጠቃሚ ማህበራዊ፣ ታሪካዊ፣ መንፈሳዊ፣ ቱሪዝም እና ስነ-ምህዳራዊ ሃብት አድርጎ ስለሚያየው ከታሪካዊ አጋሮቹ ጋር በመሆን ዥረቶችን ለማደስ የተቻላቸውን ሁሉ ማድረጉን ይቀጥላል።

ኬ ኬ ኤል-ጄ ኤን ኤፍ የእስራኤልን ጅረቶች ለህዝብ ጥቅም እና ደስታ እንዲሁም ተፈጥሮን ለመጠበቅ ይፈልጋል።
ኬ ኬ ኤል-ጄ ኤን ኤፍ የንጹህ ውሃ ጅረት መልሶ ማቋቋምን እንደ ሀገራዊ ተነሳሽነት እና እንደ ታሪካዊ ፕሮጀክት የእስራኤልን ምድር ለመቤዠት ቀጣይ ተልዕኮው አካል አድርጎ ይመለከታል።

የእስራኤል የንፁህ ውሃ ጅረቶች ሁልጊዜም የእስራኤል የባህል ገጽታ ዋና አካል ሲሆኑ የእነሱ ተሀድሶ ምድሪቱን የመቤዠት ተልእኮ የዘመናችን መግለጫ ነው።
የንጹህ ውሃ ጅረቶች እንደ ዋና፣ አሳ ማጥመድ፣ መርከብ፣ የእግር ጉዞ፣ መዝናኛ እና ጸጥ ያለ የጸሎት እና የማሰላሰል ቦታ ናቸው።
ኬ ኬ ኤል-ጄ ኤን ኤፍ የህዝቡን የተለያዩ ፍላጎቶች ለማሟላት እንዲሁም የወንዞቹን አካላዊ፣ ሀይድሮሎጂ እና ስነ-ምህዳራዊ ተግባር ለማሻሻል ይጥራል።

እያንዳንዱ ዥረት የራሱ ባህሪ እና ባህሪ አለው። ስለሆነም የእያንዳንዱን ዥረት ልዩ ባህሪ እና አካላዊ አካባቢን የሚገልጽ ዝርዝር በሆነ ማስተር ፕላን ፣ ስርዓተ-ምህዳሩን እና የአካባቢ ነዋሪዎችን ፍላጎት መሰረት ላይ የተመሰረተ የጅረት ማገገሚያ ያስፈልጋል።
ከዚህም ጋር ተያይዞ ሁሉንም የኬ ኬ ኤል-ጄ ኤን ኤፍ የመልሶ ማቋቋም ተግባራትን የሚያሳዩ እና አንድ የሚያደርጋቸው መሰረታዊ መርሆዎች አሉ።

የንጹህ ውሃ ጅረቶች የእስራኤልን የቅርብ ጊዜ እና የጥንት ዘመን ዕይታዎች ሊወክሉ ይገባል። የመልሶ ማቋቋም እንቅስቃሴ ለዚያ ዕይታ ግልፅነት፣ በሚያሳየውን ታሪካዊ ገጽታ ላይ ተጨማሪ ግብዓት መሆን አለበት። ባለፉት አመታት በተፈጠረው ፍልስፍና መሰረት የንጹህ ውሃ ጅረት መልሶ ማቋቋም አላማ የጅረቶችን ዋና ባህሪያት ለመድገም አይደለም, ይልቁንም በተፈጥሯዊ ሂደቶች በመታገዝ ስነ-ምህዳሮቻቸው እንዲያገግሙ እና ወደ ሚዛናዊ ለውጥ እነዲመጡ ማድርግ ነው።
ፎቶ: ኬኬኤል-ጄኤንኤፍ የፎቶ መዝገብ ቤት
ፎቶ: ኬኬኤል-ጄኤንኤፍ የፎቶ መዝገብ ቤት
እነዚያ በተጨናነቀው የእስራኤል ማእከል ውስጥ ያሉት የንፁህ ውሃ ጅረቶች በኬ ኬ ኤል-ጄ ኤን ኤፍ እቅድ እና አስተዳደር ውስጥ በግለሰብ እና በማህበረሰብ ደረጃ እንዲሳተፉ ማበረታታትን ያስገድዳሉ። ኬ ኬ ኤል-ጄ ኤን ኤፍ የጅረቶችን አከባቢዎች እንደ አጠቃላይ እና ውስብስብ ስነ-ምህዳሮች ይመለከታቸዋል ስለሆነም በመካከላቸው ያለው ሚዛን መጠበቅ አለበት። የእስራኤል የንፁህ ውሃ ጅረቶች በከተማ መካከል ያሉ ቀጣናዎች ወሳኝ ሚና ይጫወታሉ፥ ስለሆነም በእስራኤል ክፍት ቦታዎች እና በተገነቡ ዞኖች መካከል ያለውን ግንኙነት ለመቅረጽ ትልቅ አስተዋፅዖ ያደርጋሉ።ስለዚህ የመልሶ ማቋቋም ስራቸው መሻሻል አለበት። በመቀጠልም ይህን ልዩ የሆነ ግንኙነት ጠብቆ ማቆየት አለበት። በተጨማሪም ጅረቶች ለጎርፍ ውሃ ፍሳሽ ወሳኝ እና ወነኛ ሚና ይጫወታሉ። ስለዚህ የመልሶ ማቋቋም ስራቸው በእቅድ እና በአፈፃፀም ውስጥ ከላይ የተጠቀሱትን ሁሉንም ተግባራት ማጣመር አለበት።

የእስራኤልን የንጹህ ውሃ ጅረት መልሶ ማቋቋም በክረምቱ የሚታየውን (የጎርፍ መጥለቅለቅ) እና በደረቁ ወቅት ውሃው ቀስ በቀስ ቀነስን ታሳቢ በማድረግ የሜዲትራኒያን ባህርያቸውን መጠበቅን ይጠይቃል። ይህ ወቅታዊ የሃይድሮሎጂ ሞዴል በክልላችን ውስጥ ለሚገኙ የንፁህ ውሃ ጅረቶች ልዩ ባዮሎጂያዊ ተለዋዋጭነት መሰረት ነው። ጅረቱ የሚሄድበት መስመር በመሬቱ ልዩ ባህሪያት የታጀበ ሲሆን ይህም የዥረቱ ሥነ-ምህዳር ዋነኛ አካል ነው።

የጅረት ማገገሚያ ሂደት ለዓመታት የሚዘልቅ ሂደት ነው። ስለሆነም ስኬቱ የተመሰረተው በተፋሰሱ ዳርቻ ላይ በተደረጉ እንቅስቃሴዎች እና የብክለት መከላከል እርምጃዎች ላይ ነው። በተጨማሪም ድንበር አቋርጦ የሚሄድ ሂደት ስለሆነ በእስራኤል አስተዳደር ወይም ሉዓላዊነት ስር ባልሆኑ ክልሎች ውስጥ የሚገኙ ቦታዎችን ጨምሮ በጠቅላላው የፍሳሽ መንገድ ላይ የብክለት ምንጮችን ማየትን ይጠይቃል። ኬ ኬ ኤል-ጄ ኤን ኤፍ የውሃ ጥራትን ማሻሻልን ጨምሮ እንደ በጀት እና ሙያዊ አቅሙ የእነዚህን ተግባራት በከፊል ይወስዳል።

የእስራኤል ዥረት ባለስልጣን የተቋቋመው በ1985 ሲሆን ዓላማቸው የእስራኤልን ንጹህ ውሃ በተሳካ ሁኔታ ወደነበረበት ለመመለስ ያለሙ የተለያዩ አካላት መካከል ያለውን ትብብር ለማሳደግ የተቋቋመ ነው። እንደ አንድ ሙያዊ እውቀት እና የተግባር አቅም እንዳለው ድርጅት፣ ብሔራዊ የመልሶ ማቋቋም ጥረቱን ለመምራት እና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ለመተባበር የተዘጋጀነው። ኬ ኬ ኤል-ጄ ኤን ኤፍ የጅረት ተሀድሶን ለማራመድ ከመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ከአካባቢው መንግስታት፣ ከህዝብ ጥቅም ቡድኖች፣ ከሳይንቲስቶች እና የግል አጋሮች ጋር በጋራ ለመስራት ቁርጠኛ ሆኖ ይቀጥላል።

በዚህ መልኩ የንፁህ ውሃ ፍሰታቸው ዓመቱን ሙሉ የሚፈሱ ጅረቶችን እና በየወቅቱ የሚፈሱ ጅረቶችን መካከል ያለው መልሶ ማቋቋም መንገድ የተለየ መሆን አለበት። ዓመቱን ሙሉ ለሚፈሱ ውሃው መመለስ ሲኖርበት ለውቅታዊ ጅረቶች ግን መልሶ ማቋቋም ስራው በተፈጥሮ ስርአት ላይ ማተኮር አለበት። ምንም እንኳን የወቅታዊ ጅረቶች በባህሪያቸው ከቋሚ ጅረቶች የሚለያዩ ቢሆኑም፣ ብዙዎቹ የኬ ኬ ኤል-ጄ ኤን ኤፍ የጅረት ማገገሚያ መርሆዎች ለወቅታዊ ጅረቶች በእኩልነት ይተገበራሉ።

የኬ ኬ ኤል-ጄ ኤን ኤፍ የንጹህ ውሃ ጅረት መልሶ ማቋቋም ፖሊሲ በአራቱ የዘላቂ ልማት ማዕዘናት ላይ የተመሰረተ ነው፡- ስነ-ምህዳር፣ ኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ ደህንነት እና የትውልድ መካከል ያለውን ኃላፊነት።